Beliefs/እምነት


 

 

የእምነት መግለጫችን 

  1. መጽሐፍ ቅዱስ (ብሉይ እና ሐዲስ ኪዳን) በእግዚአብሔር መንፈስ መሪነት የተጻፉ 66 ቅዱሳት መጻሕፍትን የያዘ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን እናምናለን። እንዲሁም በሰው እምነት እና ሕይወት ላይ የመጨረሻ ሥልጣን ያለው፣ የቤተ ክርስቲያን እምነት እና ሥርዐት መሠረት እርሱ ብቻ መሆኑን እናምናለን።
  2. በዘላለማዊ፣ በማይወሰን፣ የሚታየውን እና የማይታየውን ሁሉ በፈጠረ፣ ፍጹም በማይለወጥ አንድ አምላክ፣ በእግዚአብሔር እናምናለን። ይኸውም አምላክ ሥሉስ አምላክ በመሆኑ ሦስት አካለት ሲኖሩት፣ እነዚህም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ናቸው።
  3. እግዚአብሔር አብ በፍጥረትም ሆነ በድነት ሥራ ውስጥ ጀማሪና አቃጅ መሆኑን፣ ነገር ሁሉ ከእርሱ እንደ ሆነ እና በመጨረሻም ነገር ሁሉ በእርሱ እንደሚጠቀለል እናምናለን።
  4. እግዚአብሔር ወልድ (ኢየሱስ ክርስቶስ) የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ እንደ ሆነ፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተፀንሶ ከድንግል ማርያም እንደ ተወለደ፣ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው እንደ ሆነ፣ ስለ ኃጢአታችንም በመስቀል እንደ ተሠቃየና እንደ ሞተ፣ እንደ ተቀበረ፣ በሦስተኛው ቀን ከሞት በአካል ተነሥቶ ለሰዎች እንደ ተገለጠ፣ በክብር ወደ ሰማይ እንደ ዓረገ፣ አሁንም በአባቱ ቀኝ ተቀምጦ ዘወትር ለእኛ እንደሚማልድ፣ ዳግመኛም በታላቅ ክብር እና ሥልጣን እንደሚመለስ እናምናለን።
  5. እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አጽናኝ፣ በአማኞች ውስጥ አድሮ መንፈሳዊ ስጦታዎችን እና ኀይልን በመስጠት ቤተ ክርስቲያንን ቀዳሽ፣ እንደዚሁም ስለ ኀጢአት፣ ስለ ጽድቅ እና ስለ ፍርድ ዓለምን ወቃሽ እንደ ሆነ እናምናለን።
  6. አዳም እና ሔዋን በእግዚአብሔር አምሳል መፈጠራቸውን፣ በኋላም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መጣሳቸው ይህም በሰው ዘር ሁሉ ላይ ውድቀትን ማስከተሉን፣ ከዚህም የተነሣ ሰዎች ሁሉ ኀጢአትን ስለሚያደርጉ እና ስለሚበድሉ የእግዚአብሔር ቁጣ እና ፍርድ ያለባቸው መሆኑን እናምናለን።
  7. ድነት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን በጸጋ ብቻ የሚገኝ እንጂ በሌላ በማንም ወይም በምንም እንደማይገኝ እናምናለን። ስለሆነም ሰዎች በኀጢአታቸው ተጸጽተው ንስሓ ቢገቡና ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኛቸው እና ጌታቸው አድርገው ቢቀበሉ ከመንፈስ ቅዱስ እንደሚወለዱ እና የእግዚአብሔር ልጅነትን ሥልጣን እንደሚቀበሉ እናምናለን።
  8. በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም በሚደረግ የአማኝ የውሃ ጥምቀት እናምናለን። በተጨማሪም በኤፌሶን 5፥18 መሠረት የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ዛሬም በጸሎት እና በጉጉት ልንጠብቀው የተገባ፣ በክርስቶስ የተሰጠን ትእዛዝ በመሆኑ አማኞች የመንፈስ ቅዱስ ስጦታን እንድንቀበል እና መንፈስ ቅዱስ እንደ ወደደ በሚሰጠው መጠን በልዩ ልዩ ቋንቋ (ልሳን) አማኞች እንደሚናገሩ እናምናለን።
  9. አማኞች የምንካፈለው የጌታ እራት ጌታ ዳግም እስኪመጣ ድረስ ፍቅሩን እና ሞቱን የምናስብበት፣ ራሳችንን የምንመረምርበት፣ ሞቱን እና ትንሣኤውን ለማብሰር ቃል የምንገባበት ሥርዐት እንደ ሆነ እናምናለን።
  10. በአማኞች አካላዊ ትንሣኤ እና ንጥቀት እናምናለን። እንዲሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መንግስቱን በሙላት ሊመሠርት ከቅዱሳኑ ጋር ተመልሶ ወደ ምድር እንደሚመጣ፣ የሙታን ሁሉ ትንሣኤ እንደሚኖርና የመጨረሻው ፍርድ እንደሚካሄድ፣ ከዚያም ኀጢአተኞች ከእግዚአብሔር ተለይተው የዘላለም ቅጣታቸውን እንደሚቀበሉ፣ ጻድቃን ግን ከእርሱ ጋር በዘላለም ሕይወት በደስታ እንደሚኖሩ እናምናለን።

 

Our Statement of Faith 

  1. We believe that the Bible (the Old and New Testament) is made of 66 books written by the guidance of Holy Spirit; that is has the ultimate authority on the life and faith of an individual and church conduct. 
  2. We believe in an eternal, limitless, Creator of the seen and unseen, forever unchanging one true God, who is triune; the three personhoods are the Father, the Son and the Holy Spirit. 
  3. God the Father is the One who planned and originated creation and the work of salvation; all things come from Him and in Him it will be finished. 
  4.  God the Son, Jesus Christ, is the one and only Son of God, who by the Holy Spirit was conceived in the womb of the virgin Mary; He is 100% God and 100% man. He went onto a cross to die for our sins, was buried and 3 days later was resurrected and revealed to His disciples. In glory, He ascended to heaven and is seated on the right hand of the Father, where He intercedes on our behalf. And again, He will return in glory and authority to the earth. 
  5. God the Holy Spirit, the Comforter, dwells in each and every believer and gifts to every Christian spiritual gifts and power to facilitate and empower the church to holiness. Regarding sin, righteousness, and judgement, He functions as a witness to the world. 
  6. We believe that Adam and Eve were created in the likeness of God, then disobeyed the commands of God, thereby the capacity to sin has descended throughout all mankind. As a result, since all mankind have sinned and continue to sin, we are deserving of the judgement of God. 
  7.  We believe that salvation is through Jesus Christ by grace and through faith alone; salvation cannot be attained by any other means. As an individual acknowledges their sin, repents and accepts Jesus Christ as their Saviour and Lord, they are born again by the Holy Spirit being made a child of God. 
  8.  We believe in water baptism being done in the name of the Father, the Son, and the Holy Spirit via immersion. Moreover, according to Ephesians 5:18, we are to eagerly seek the filling of the Holy Spirit through prayer. Since it is commands given to us by Jesus Christ Himself, believers are to receive the gifts of the Holy Spirit which are distributed as the Spirit pleases. As such we also believe that the Spirit still gives the gift of Tongues to this day 
  9. Believers are to partake in the Lord’s Supper until Christ returns to proclaim His death and resurrection, as we do so we introspectively examine ourselves, and meditate on His love and death on the cross. 
  10. We believe that upon the resurrection and rapture all believers will receive a new incorruptible body. Our Lord Jesus Christ will come with all the saints to fully establish His Kingdom on the earth. All those who have died will be resurrected where there will be a final judgement to be received. Therein, sinners who have remained separate from God will then receive their eternal judgement, but the saints will enjoy eternal life with God forever.